Fedral Dimocratic Republic of Ethiopia, Ministry of Finance

All News

None

ኢትዮጵያን የምስራቅ አፍሪካ የታዳሽ ሀይል ምንጭ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ

የካቲት 25 / 2014 ዓ.ም - በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ትኩረት በተሰጠው የኢነርጂ ዘርፍ ኢትዮጵያን የምስራቅ አፍሪካ የታዳሽ ሀይል ምንጭ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አቶ አህመድ ሺዴ ገለጹ፡፡ 

None

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባለፉት ስድስት ወራት ከ58 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱ ተገለጸ፡፡

የካቲት 22 2014 ዓ.ም - የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የግማሽ አመት የስራ አፈጻጸም በገንዘብ ሚኒስቴርና በመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳር በሂልትን ሆቴል በተገመገመበት ወቅት እንደተገለጸው ባንኩ ከሀምሌ 2013 እስከ ታህሳስ 2014 ዓ.ም ባሉት ስድሰት ወራት ውስጥ 58.1 ቢሊዮን ብር ገቢ አግኝቷል፡፡

None

ኢትዮጵያና ጣሊያን የአንድ ሚሊዮን ዩሮ የእርዳታ ስምምነት ተፈራረሙ

የካቲት 22 2014ዓ.ም - ኢትዮጵያና ጣሊያን ለዜጎች መረጃ ምዝገባ አገልግሎት የሚውል የአንድ ሚሊዮን ዩሮ ( 56,967,900 ብር ) የእርዳታ ስምምነት በሂልተን ሆቴል ተፈራረሙ፡፡

None

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በአስቸጋሪ ወቅትም በውጤታማነቱ መዝለቁ ተገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የስድስት ወር የስራ አፈፃፀም በገንዘብ ሚኒስቴርና በመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ዛሬ የካቲት 22 2014 ዓ.ም በሂልተን ሆቴል በተገመገመበት ወቅት የድርጅቱ ምክትል ዋና ስራ አሰፈፃሚ አቶ ኢሳያስ ወልደ ማሪያም እንዳስታወቁት ድርጅቱ ከመሰል ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ድርጅቶች አንጻር በተለያዩ መመዘኛዎች ሲታይ የላቅ ዕድገት አሳይቷል፤ ትርፋነቱም በዚህ አስቸጋሪ ወቅትም ቀጥሏል ብለዋል፡፡

None

ኢትዮ ቴሌኮም የደንበኞቹ ቁጥር ከ60 ሚሊየን ማለፋን አስታወቀ

የኢትዮ- ቴሌኮም የግማሽ ዓመት አፈፃፀም ዛሬ የካቲት 21 2014 ዓ.ም በሂልተን ሆቴል በገንዘብ ሚኒስቴርና በመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር በተገመገመበት ወቅት የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ የድርጅታቸው አጠቃላይ የደንበኞች ቁጥር 60 ነጥብ 8 ሚሊየን መድረሱን አስታውቀዋል፡፡

None

የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን ማዘመንና የበለጠ ውጤታማ ማድረግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር ለማድረግ የሚያስችል ጉብኘት ተደረገ

በገንዘብ ሚኒስቴር ዴኤታ በክብርት ወ/ሮ ሰመሬታ ሰዋሰው የተመራ ልዑክ በኦሮሚያ እና በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስታት ስር የሚገኙት የቡልቡላ እና የይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን ጎብኝቷል፡፡

None

የገንዘብ ሚኒሰቴር ያዘጋጀውን የህጻናት ማቆያ አስመረቀ

የገንዘብ ሚኒሰቴር ለሰራተኞቹ ልጆች ያዘጋጀውን ሕፃናት ማቆያ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በይፋ አስመርቋል፡፡ የህፃናት ማቆያው ከ4 ወር- 3 ዓመት ዕድሜ ክልል ውስጥ ላሉ ልጆች አገልግሎት ይሰጣል፡፡

None

በክቡር አቶ አህመድ ሺዴ የተመራው የልኡካን ቡድን ከሳውዲ ባለስልጣናት ጋር መከረ፡፡

በገንዘብ ሚኒስትር ክቡር አቶ አህመድ ሺዴ የተመራው የኢትዮጵያ የልኡካን ቡድን ከሳውዲ አረቢያ የንጉስ ሰልማን የሰብአዊ እርዳታ ማእከል የበላይ ሀላፊ ከክቡር ዶ/ር አብዱላህ አልራቢሀ ጋር በሁለቱ ሀገራት የጋራ ሰብአዊና የእርዳታ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡

None

በኢትዮጵያ ፕሮጀክት በጋራ መቆማችንን ማረጋገጥ እንደሚገባ ተገለጸ

ሁሉም ኢትዮጵያዊ ኢትዮጵያ ለተሰኘች ውብ ፕሮጀክት እውን መሆን በጋራ መቆም አንደሚገባውና ለልጆቻችን የተሸለች ኢትዮጵያን ማውረስ እንደሚጠበቅብን የገንዘብ ሚኒስቴር የፖሊሲ ጉዳዮች ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር እዮብ ተካለኝ ገለጹ፡፡

None

ባለፉት ሶስት ወራት በመንግስት ገቢና ወጪ ረገድ ጤናማ የፊሲካል አስተዳደር ተግባራዊ መደረጉ ተገለጸ፡፡

በ2014 በጀት አመት 2ኛ ሩብ ዓመት (ከጥቅምት-ታህሳስ) የ100 ቀን እቅድ አፈጻጸም በገንዘብ ሚኒስቴር በተገመገመበት ወቅት እንደተገለጸው በፌዴራል መንግስት ከሀገር ውስጥና ከልማት አጋሮች ለመሰብሰብ የታቀደውን የመንግስት ገቢ ለማሳካት ከፍተኛ ጥረት የተደረገ ሲሆን፣ አፈጻጸሙም መልካም እንደነበር ተመልክቷል፡፡