የካቲት 25 / 2014 ዓ.ም - በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ትኩረት በተሰጠው የኢነርጂ ዘርፍ ኢትዮጵያን የምስራቅ አፍሪካ የታዳሽ ሀይል ምንጭ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አቶ አህመድ ሺዴ ገለጹ፡፡
የካቲት 22 2014 ዓ.ም - የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የግማሽ አመት የስራ አፈጻጸም በገንዘብ ሚኒስቴርና በመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳር በሂልትን ሆቴል በተገመገመበት ወቅት እንደተገለጸው ባንኩ ከሀምሌ 2013 እስከ ታህሳስ 2014 ዓ.ም ባሉት ስድሰት ወራት ውስጥ 58.1 ቢሊዮን ብር ገቢ አግኝቷል፡፡
የካቲት 22 2014ዓ.ም - ኢትዮጵያና ጣሊያን ለዜጎች መረጃ ምዝገባ አገልግሎት የሚውል የአንድ ሚሊዮን ዩሮ ( 56,967,900 ብር ) የእርዳታ ስምምነት በሂልተን ሆቴል ተፈራረሙ፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የስድስት ወር የስራ አፈፃፀም በገንዘብ ሚኒስቴርና በመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ዛሬ የካቲት 22 2014 ዓ.ም በሂልተን ሆቴል በተገመገመበት ወቅት የድርጅቱ ምክትል ዋና ስራ አሰፈፃሚ አቶ ኢሳያስ ወልደ ማሪያም እንዳስታወቁት ድርጅቱ ከመሰል ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ድርጅቶች አንጻር በተለያዩ መመዘኛዎች ሲታይ የላቅ ዕድገት አሳይቷል፤ ትርፋነቱም በዚህ አስቸጋሪ ወቅትም ቀጥሏል ብለዋል፡፡
የኢትዮ- ቴሌኮም የግማሽ ዓመት አፈፃፀም ዛሬ የካቲት 21 2014 ዓ.ም በሂልተን ሆቴል በገንዘብ ሚኒስቴርና በመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር በተገመገመበት ወቅት የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ የድርጅታቸው አጠቃላይ የደንበኞች ቁጥር 60 ነጥብ 8 ሚሊየን መድረሱን አስታውቀዋል፡፡
በገንዘብ ሚኒስቴር ዴኤታ በክብርት ወ/ሮ ሰመሬታ ሰዋሰው የተመራ ልዑክ በኦሮሚያ እና በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስታት ስር የሚገኙት የቡልቡላ እና የይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን ጎብኝቷል፡፡
የገንዘብ ሚኒሰቴር ለሰራተኞቹ ልጆች ያዘጋጀውን ሕፃናት ማቆያ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በይፋ አስመርቋል፡፡ የህፃናት ማቆያው ከ4 ወር- 3 ዓመት ዕድሜ ክልል ውስጥ ላሉ ልጆች አገልግሎት ይሰጣል፡፡
በገንዘብ ሚኒስትር ክቡር አቶ አህመድ ሺዴ የተመራው የኢትዮጵያ የልኡካን ቡድን ከሳውዲ አረቢያ የንጉስ ሰልማን የሰብአዊ እርዳታ ማእከል የበላይ ሀላፊ ከክቡር ዶ/ር አብዱላህ አልራቢሀ ጋር በሁለቱ ሀገራት የጋራ ሰብአዊና የእርዳታ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡
ሁሉም ኢትዮጵያዊ ኢትዮጵያ ለተሰኘች ውብ ፕሮጀክት እውን መሆን በጋራ መቆም አንደሚገባውና ለልጆቻችን የተሸለች ኢትዮጵያን ማውረስ እንደሚጠበቅብን የገንዘብ ሚኒስቴር የፖሊሲ ጉዳዮች ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር እዮብ ተካለኝ ገለጹ፡፡
በ2014 በጀት አመት 2ኛ ሩብ ዓመት (ከጥቅምት-ታህሳስ) የ100 ቀን እቅድ አፈጻጸም በገንዘብ ሚኒስቴር በተገመገመበት ወቅት እንደተገለጸው በፌዴራል መንግስት ከሀገር ውስጥና ከልማት አጋሮች ለመሰብሰብ የታቀደውን የመንግስት ገቢ ለማሳካት ከፍተኛ ጥረት የተደረገ ሲሆን፣ አፈጻጸሙም መልካም እንደነበር ተመልክቷል፡፡
Copyright © 2025 MOF All Right Reserved